ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ — መጽሐፈ ምስጢር

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

የ14ኛው ክ/ዘመን ታላቅ ኢትዮጵያዊ ሊቅ

ስለ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ

ጸሐፊ፣ መምህርና መንፈሳዊ አባት — በ1357 ዓ.ም በወሎ ከላላ ወረዳ ሸግላ (ሰግላ) ተወለዱ። በጥቅምት 3 ተፀንሰው፣ በሐምሌ 7 ተወለዱ። ከአባታቸው የመጀመሪያ ትምህርት በኋላ ወደ ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ — ከአባ ሠረቀ ብርሃን ቤተ-ጉባኤ ተማሩ።

በነሐሴ 21 እመቤታችን ጽውዐ ልቡና አጠጣቻቸው። የንጉሥ ዳዊት ስምንት ልጆች መምህር ሆኑ፤ ማኅሌት ደረሱ። ከአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገብተው መነኰሱ — ደብረ ባሕርይ ጋስጫን መሰረቱ።

መጽሐፈ ምስጢር፣ መጽሐፈ ሰዓታትና ሌሎች ብዙ ድርሰቶች — «ብርሃን ኢትዮጵያ» ተብለው ይታወቃሉ። ዋሻ፣ ድልድይና የውኃ ማቈሪያዎች ሠሩ።

በ1417 ዓ.ም በሐምሌ 7 ቀን ዐረፉ። ጌታችን ቃል ኪዳን ሰጣቸው። ሥጋቸው በደብረ ባሕርይ ጋስጫ ገዳም ተቀመጠ — የ600ኛ የእረፍት በዓላቸውን ዛሬም እናከብራለን።

ሙሉ ታሪክ

የብርሃን መጽሐፍት

«ብፁዕ ጊዮርጊስ የብሉይና የሐዲሳት ፍሬን ይሰበስባል»

መጽሐፈ አርጋኖን — የመጽሐፍ ምስል
መጽሐፈ አርጋኖን
መጽሐፈ ሰዓታት — የመጽሐፍ ምስል
መጽሐፈ ሰዓታት
ውዳሴ መስቀል — የመጽሐፍ ምስል
ውዳሴ መስቀል
መጽሐፈ ምስጢር — የመጽሐፍ ምስል
መጽሐፈ ምስጢር
መጽሐፈ ብርሃን — የመጽሐፍ ምስል
መጽሐፈ ብርሃን
መዓዛ ቅዳሴ — የመጽሐፍ ምስል
መዓዛ ቅዳሴ
ኆኅተ ብርሃን — የመጽሐፍ ምስል
ኆኅተ ብርሃን
መጽሐፈ አርጋኖን — የመጽሐፍ ምስል
መጽሐፈ አርጋኖን
መጽሐፈ ሰዓታት — የመጽሐፍ ምስል
መጽሐፈ ሰዓታት
ውዳሴ መስቀል — የመጽሐፍ ምስል
ውዳሴ መስቀል
መጽሐፈ ምስጢር — የመጽሐፍ ምስል
መጽሐፈ ምስጢር
መጽሐፈ ብርሃን — የመጽሐፍ ምስል
መጽሐፈ ብርሃን
መዓዛ ቅዳሴ — የመጽሐፍ ምስል
መዓዛ ቅዳሴ
ኆኅተ ብርሃን — የመጽሐፍ ምስል
ኆኅተ ብርሃን

የሕይወት ጊዜ መስመር

1357 ዓ.ም1417 ዓ.ም

1357 ዓ.ም
1/7

ሰግላ · ከለላ · ወሎ

ፅንሰትና ልደት

በቤተ አምራ (አሁን ወሎ) በከለላ ወረዳ ሸግላ (ሰግላ) ተወለዱ። በጥቅምት 3 ቀን 1357 ዓ.ም ተፀንሰው፣ በሐምሌ 7 ተወለዱ። አባታቸው ሕዝበ ጽዮን — የቤተ መንግሥት ባለሟል፣ ጠቢብና የሰግላ ሀገረ ገዥ — እናታቸውም እምነ ጽዮን ናቸው። ሁለቱም እንደ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ በእግዚአብሔር ሕግ ጸንተው ሲኖሩ ልጅ አልነበራቸውም። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከመልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ጋር ተገልጻ ጸሎታቸውን ተቀብላ የተባረከ ልጅ እንደሚወልዱ፣ ስሙንም እንደ ሰማእታት አለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስ «ጊዮርጊስ» እንዲሰይሙ አዘዘቻቸው።

2/7

ሰግላ · ሐይቅ እስጢፋኖስ

ትምህርትና ዲቁና

የመጀመሪያ ትምህርታቸው ከአባታቸው ሕዝበ ጽዮን ነበር። በአፄ ዳዊት ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ወደ ጳጳስ አቡነ ሰላማ መተርጉም ወስደው ዲቁና ማዕረግ አሾሟቸው። ከዚያም በንጉሥ ዳዊት ዘመን (1378 - 1405 ዓ.ም) ወደ ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም ሄደው ከታላቁ ሊቅ ዓቃቤ ሰዓት አባ ሠረቀ ብርሃን ቤተ-ጉባኤ ተማሩ። የቀለም ትምህርት ቶሎ አልያዙም — ከትምህርት ይልቅ የገዳሙን አበው መርዳትና የብሕትውናን ሕይወት ይመርጡ ነበር። ጓደኞቻቸው ሲቀድሟቸው አዝነው በእንባና በጾም ከእመቤታችን ሥዕል ፊት ጥበብን ለመኑ።

3/7

ወላዲተ አምላክ

ጽውዐ ልቡና

እመቤታችን ወላዲተ አምላክ በነሐሴ 16 ቀን ተገልጻ ራሳቸውን እንዲያነጹ፣ ነፍሳቸውን እንዲቀድሱና ቀጠሮ እንዲጠብቁ አዘዘቻቸው። በነሐሴ 21 ቀን ከኪሩቤል፣ ሱራፌልና መላእክት ጋር ተመልሳ መጣች። ቅዱስ ሚካኤል በቀኟ፣ ቅዱስ ገብርኤል በግራዋ ቀረቡ። እመቤታችን ከእውቀት ወንዝ የመጣ ንጹሕ ጽዋ አጠጣቻቸው — ያ ጽዋ ጽውዐ ልቡና ነው። የሰማይና የምድር ምስጢር ተገለጸላቸው፤ በእግዚአብሔር ፈቃድ ቤተ ክርስቲያን የምትገለገልባቸው ብዙ ቅዱሳን መጻሕፍትን ደረሱ።

4/7

ዓፄ ዳዊት

ቤተ መንግሥት

ዓፄ ዳዊት ሊቅነታቸውን አውቀው ወደ ቤተ መንግሥት አስጠርተው ከበረሯቸው። የስምንቱ ልጆቻቸው መምህር አደረጓቸው — ከነሱም ቅዱስ የተባለው ንጉሥ ቴዎድሮስ፣ እንድርያስ፣ ይሥሐቅ፣ ንግሥት እሌኒና ዘርአ ያዕቆብ ይገኛሉ። ለነገሥታት፣ ካህናትና መሳፍንት አስተማሪ ሆኑ። ማኅሌት ደረሱ፤ ከጋርማዊው አቡነ ሳሙኤል ዜማን ተምረዋል። ዓፄ ዳዊት በጋብቻ ሊያስሹዋቸው ፈልገው ነበር — እሳቸው ግን የመንግሥተ ሰማያት ጃንደረባ ማድረግን መረጡ።

5/7

በጸሎተ ሚካኤል · ዓፄ ይሥሐቅ

ደብረ ባሕርይ ጋስጫ

የአመክሮ ጊዜያቸውን ሲጨርሱ ከታላቁ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው መነኰሱ። በማኅበሩ ራስ ሆነው ደብረ ባሕርይ ጋስጫ ገዳምን መሰረቱ — የተመሠረተበት ዘመን ከአስተማሯቸው ነገሥታት በአንዱ በዓፄ ይሥሐቅ ዘመን ነው። ዋሻ ቤተ ክርስቲያን ፈልፍለው፣ የውኃ ማቈሪያዎች ቈፈሩ፣ ድልድይ ሠሩ። በትምህርታቸው የተመሠጡ ሊቃውንት «ዳግማይ ዮሐንስ አፈወርቅ» ሲሏቸው፣ ዓፄ ይሥሐቅም «ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ» ብለው ሰይመዋቸዋል።

6/7

ብርሃን ኢትዮጵያ

መጽሐፈ ምስጢር

መጽሐፈ ምስጢር፣ መጽሐፈ ሰዓታት፣ አርጋኖን፣ ውዳሴ መስቀል፣ መጽሐፈ ፈውስ፣ መጽሐፈ ባሕርይና ሌሎች ብዙ ድርሰቶች ጻፉ። መጽሐፈ ምስጢር ከእረፍታቸው በፊት በሁለት ዓመት አካባቢ ተጠናቀቀ። በገድላቸው «ብርሃን ኢትዮጵያ» እና «ያሬድ ሁለተኛ» ተብለው ይታወቃሉ — እስከ ዛሬም በሀገራችን አምሳያ የላቸውም።

7/7

ሐምሌ 7 · ጋስጫ

እረፍትና ቃል ኪዳን

ቆመው እየጸለዩ ሳሉ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችንና ከቅዱሳን ጋር ተገልጦ ቃል ኪዳን ሰጣቸው — የገዳሙን ልጆች፣ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች፣ የገድሉን ጸሐፊዎችና አድማጮች እንደሚምራቸው። በስድሳኛው ዓመታቸው በ1417 ዓ.ም በሐምሌ 7 ቀን ዐረፉ። ቅድስት ነፍሳቸው በይባቤ መላእክት ዐረገች፤ ደቀ መዛሙርትም ሥጋቸውን በደብረ ባሕርይ ጋስጫ ገዳም አኖሩ።

ሙሉ ገድለ ታሪክ

ቅዱስ ቀናት

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

ዓመታዊ በዓላት — ለጸሎት፣ ለመታሰቢያና ለምስጋና።

ሁሉንም በዓላት

01

ጥቅምት 3

የተፀነሱበት ቀን

03

ነሐሴ 21

ጽውዐ ልቡና

ትኬት

600ኛ የእረፍት በዓል

የበዓሉን ትኬት በ Telegram ይግዙ። ክፍያ በCBE — ትኬትዎ በቦቱ ላይ በQR ይደርስዎታል።

  • በ Telegram ይግዙ
  • QR በመግቢያ
  • CBE ባንክ ክፍያ

Telegram

ትኬትዎን አሁኑኑ ያግኙ

300 ብርለአንድ ትኬት

በ Telegram · CBE ባንክ ክፍያ